የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ-10 አስተዳደር ፋይናንስ ጽ/ቤት በ2018 በጀት ዓመት የ2ኛ ዙር በወረዳው ጽ/ቤቶች ከዚህ በታች በሎት የተዘረዘሩትን እቃዎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ-10 አስተዳደር ፋይናንስ ጽ/ቤት በ2018 በጀት ዓመት የ2ኛ ዙር በወረዳው ጽ/ቤቶች ከዚህ በታች በሎት የተዘረዘሩትን እቃዎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
ሎት 1 - አላቂ እቃዎች, ሎት 2- የደንብ ልብስ, ሎት 3 - የጽዳት እቃዎች, ሎት 4 - ድንኳን ኪራይ
ሎት 5- -የተሽከርካሪ ጎማዎች, ሎት 6 - ስፌት
ስለሆነም በጨረታው መሳተፍ የሚፈልግ የሚከተለ‐ትን መስፈርቶች አሟልቶ በጨረታው መወዳደር ይችላል።
1. ከዘርፉ ጋር ተያያዥ የንግድ ፍቃድ ያላቸውና ማስረጃ ማቅረብ የሚችል
2. በዘመኑ የታደሰ ንግድ ፍቃድ ያላቸው
3. የዘመኑን ግብር የከፈለና የአቅራቢነት ምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችል
4. 100,000 (አንድ መቶ ሺህ ብር) በላይ ከተጫረቱ የተጨማሪ እሴት ታክስ የተመዘገቡበት ማስረጃ ፎቶ ኮፒ ማያያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
5. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (ቲን ነምበር) ማቅረብ አለባቸዉ፡፡
6. ጥቃቅንና አነስተኛ የተደራጁትን የምናስተናግደው ባመረቱት ምርት ብቻ በመመሪያው መሰረት ይሆናል።
7. የጨረታው አሸናፊ ድርጅት የውል ማስረከቢያ ጨረታው ያሸነፈበት መጠን 10% ማስያዝ አለበት፡፡
8. ማንኛውም ህጋዊ ተጫራች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ የማይመለስ ብር 300.00 በመክፈል የጨረታ ሰነዱን ዘወትር በስራ ሰዓት በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 10 አስተዳደር ፋይናንስ ጽ/ቤት 2ኛ ፎቅ መውሰድ ይችላሉ ተጫራቶች የጨረታ ማስከበሪያ 0.5 ማለትም ሎት 1 2,000፣ ሎት 2 3,000፣ ሎት 3 2,000፣ ሎት 4 1,500፣ ሎት 5 1,800 እና ሎት 6 1,700 በሚል pay/order Addis Ketemak/K Wereda 10 F/TS/ BET በሚል ስም የተዘጋጀ በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
9. ተጫራቾች ስለእቃዎች ማለትም ለሎት 1,2,3 ሳምፕል ማቅረብ እና ቀሪው ሎት በተጠቀሰው ስፔስፊኬሽን ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል ሳምፕል ያላቀረበበትን እቃ የማናወዳድር መሆኑን እየገለፅን ሳምፕሉ ጨረታው ከመከፈቱ ቢያንስ ከ3ቀን በፊት በመዳበሪያ መቅረብ አለበት ከተጠቀሰው ቀን ዘግይተው የሚመጡ ሳምፕሎች ተቀባይነት አይኖራቸዉም፣
10. የሚገቡት ዋጋዎች ቫት ያካተቱ መሆን አለባቸው።
11. ተጫራቾች በገዙት ሰነድ መሰረት የሚወዳደረበት ዋጋ ከላይ የተጠቀሱትን ደጋፊ ሰነዶች 1 ኦሪጂናልና 1 ኮፒ በአንድ ላይ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ በማድረግ ጨረታ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ የስራ ቀናት በተዘጋጀው የማወዳደሪያ ጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
12. ተጫራቾች ጨረታውን ካሸነፉ በኋላ ያሸነፋበትን ዕቃ በወረዳው ፅ/ቤት ንብረት ክፍል ድረስ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል
13. ጨረታው ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ11ኛው የስራ ቀን ተዘግቶ በ11ኛው ቀን ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸዉ በተገኙበት ከጠዋቱ 4:00 ሰዓት ተዘግቶ 4:30 ይከፈታል፡፡
14. መ/ቤቱ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነዉ፣፣
15. ተጫራቾች ጨረታውን ካሽነፋ በኋላ ያሸነፉበትን የጨረታ አይነት ውል አይገባም ቢሉ ያስያዙትን የጨረታ ማስከበሪያ ውርስ የሚደረግ እና ለተወሰኑ ወራቶች የትኛዉም የመንግስት መሰሪያ ቤት እንዳይሳተፋ የሚደረግ መሆኑን እንገልጻለን፡፡
አድራሻ፡- አዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 10 አስተዳደር ፋይናንስ ጽ/ቤት አጠና ተራ ከድልድዩ ከፍ ብሎ ለበለጠ መረጃ፡- 01122739821 በመደወል ማግኘት ይችላሉ፡፡
የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ-10 አስተዳደር ፋይናንስ ጽ/ቤት
