በን/ስ/ሳ/ከ/ከ/ወረዳ 09 የሚገኘው የአዲስ አምባ አፀደ ህፃናትና የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት ለ2019 በጀት ዓመት የሚያስፈልገውን ቋሚ እቃዎች፤ አላቂ የቢሮ አቃዎች፤ አላቂ የትምህርት አቃዎች፤ የፅዳት አቃዎች፤ የደንብ ልብስ፤ የጥገና አቃዎች፤ ቤተ-መጻህፍት በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
በን/ስ/ሳ/ከ/ከ/ወረዳ 09 የሚገኘው የአዲስ አምባ አፀደ ህፃናትና የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት ለ2019 በጀት ዓመት የሚያስፈልገውን ቋሚ እቃዎች፤ አላቂ የቢሮ አቃዎች፤ አላቂ የትምህርት አቃዎች፤ የፅዳት አቃዎች፤ የደንብ ልብስ፤ የጥገና አቃዎች፤ ቤተ-መጻህፍት በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
ስለሆነም በጨረታው ለመሳተፍ የምትፈልጉ ከዚህ በታች በዝርዝር የቀረቡትን መስፈርት የምታሟሉ ተጫራቾች በሙሉ በጨረታው እንድትሳተፉ አንጋብዛለን፡፡
- እቃውን በጥራት ለማቅረብ የሚያስችል ብቃት፤ ሕጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸውና የታደሰ ንግድ ፈቃድ ያላቸው፡፡
- ተጫራቾች በአቅራቢዎች ዝርዝር ውስጥ የተመዘገቡና የምስክር ወረቀት ኮፒ ከጨረታ ሰነዱ ጋር አያይዘው ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች በተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) ተመዝጋቢ የሆኑና ለዚህም የተመዘገቡበትን ኮፒ አያይዘው ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ የጠቅላላ ዋጋውን ብር 15,000 (አስራ አምስት ሺ ብር) በባንክ በተረጋገጠ ሰነድ (CPO) ከጨረታው ሰነድ ጋር በፖስታ በማሸግ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ብር 150 (አንድ መቶ ሀምሳ ብር ብቻ) በመክፈል ሰነዱን ከአዲስ አምባ የመ/ደ/ት/ቤት ፋይናንስ ቢሮ ቁጥር 05 ከፍል ቀርበው በ 10 (አስር) ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ መግዛት ይገላሉ፡፡
- ተጫራቾች ለሚጫረቱበት እቃ ናሙና የማቅረብ ግዴታ አለባቸው፡፡
- ተጫራቾች በገዙበት የጨረታ ሰነድ ላይ በተዘጋጀው የዋጋ ዝርዝር መሙያ ላይ ሞልተው ማቅረብ አለባቸው፡፡ በሌላ ሰነድ ከሞሉ ተቀባይነት የለውም፡፡
- ባቀረቡት ዋጋ ዝርዝር ላይ ቫት (VAT) ማካተት አለባቸው፡፡
- ጨረታው ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ታትሞ አየር ላይ ከዋለበት ቀን ጀምሮ እስከ 10 የሥራ ቀን አየር ላይ ውሎ በ10ኛው ቀን 11 ሰዓት ላይ ታሽጎ በዚያው ቀን ከጠዋቱ በ 4 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ባሉበት በት/ቤቱ ፋይናንስ ክፍል ይከፈታል፡፡ ነገር ግን ተጫራቾች ወይም ወኪሎቻቸው ባይገኙም የጨረታው ሂደት በተቀመጠው መሰረት ይካሄዳል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የሚጫረቱበትን የመወዳደሪያ ዋጋ ሞልተው በታሸገ ፖስታ ውስጥ አድርገው ማቅረብ አለባቸው፡፡
- ከጥቃቅንና አነስተኛ ድርጅቶች ደብዳቤ ይዘው የሚመጡ ተጫራቾች ካደራጃቸው አካል ደብዳቤ ሲያመጡ የተደራጁበትን ዘርፍ ተጠቅሶ ቀጥታ በት/ቤቱ ስም ማናፍ አለበት፡፡ የጨረታ ማስከበሪያ (CPO) የሰነድ መግዣ ዋጋ እና የውል ማስከበሪያ በነፃ መውሰድ እንደሚችሉ ተጠቅሶ መናፍ አለበት፡፡
- ትምህርት ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
አድራሻ፡- በን/ስ/ሳ/ከ/ከ/ወረዳ 09 የሚገኘው የአዲስ አምባ አፀደ ህፃናትና የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት አዲስ ሰፈር ድልድይ ወረድ ብሎ አዲስ ሰፈር ጣና ገበያ ፊት ለፊት፡፡
ለተጨማሪ መረጃ፡- በስልክ ቁጥር 09-42-04-41 | 09-70-70-17 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡
በን/ስ/ሳ/ከ/ከ/ወረዳ 09 የሚገኘው የአዲስ አምባ አፀደ ህፃናትና የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት
✨ messages.ai_summary
Addis Amba Orphanage and Primary School seeks suppliers for fixed assets, consumable office and educational materials, cleaning supplies, uniforms, maintenance items, and library materials. Bidders must have a valid renewed business license, be registered on the suppliers list, be VAT-registered, and provide samples.
