ዲ.ኤም.ሲ ኮንስትራክሽን ኃላ/የተ/የግ/ማህበር እያሰራቸው በሚገኙ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ላይ ሲጠቀምባቸው የነበሩ የተለያዩ የኮንስትራክሽን ተረፈ ምርቶችን ማለትም ለአስፋልት ስራ ተጠቅሞ የተረፈ የሬንጅ /Bitumen/ በርሜል እንዲሁም የሲሚንቶ ከረጢት በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡
ዲ.ኤም.ሲ ኮንስትራክሽን ኃላ/የተ/የግ/ማህበር
1. ዲ.ኤም.ሲ ኮንስትራክሽን ኃላ/የተ/የግ/ማህበር እያሰራቸው በሚገኙ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ላይ ሲጠቀምባቸው የነበሩ የተለያዩ የኮንስትራክሽን ተረፈ ምርቶችን ማለትም ለአስፋልት ስራ ተጠቅሞ የተረፈ የሬንጅ /Bitumen/ በርሜል እንዲሁም የሲሚንቶ ከረጢት በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡
2. በጨረታው ላይ ለመሳተፍ የሚፈልጉ ድርጅቶች አግባብነት ካለው መንግስት አካል ለ2018ዓም የታደስ የንግድ እና ታክስ ክሊራንስ ሰርተራኬት ማሟላት አለባቸው:: ፍቃድ፣ ግብር ከፋይ መለያ ቁጥር /TIN Number/ ተጨማሪ እሴት ታክስ ከፋይ መሆናቸውን የሚያሳይ ማስረጃ
3. ንብረቶቹ የሚገኙበት ቦታ፡-
➢ የራንጅ /Bitumen/ በርሜል የሚገኘው በአማራ ብሄራዊ ክልል ምዕራብ ጎጃም ዞን ሰከላ ወረዳ በድርጅቱ የመንገድ
ስራ ፕሮጀክት ካምፕ ውስጥ ነው:: ➢ የሲሚንቶ ከረጢቱ የሚገኘው በአዲስ አበባ ከተማ ን/ስ/ላ ክፍለ ከተማ ለበ መብራት ኃይል የዲ ኤም.ሲ ሪል
እስቴት ጊቢ ውስጥ ነው::
4. ተጫራቾች ሊገዙት ያሰቧቸውን እቃዎች ጠቅላላ ዋጋ 10% የጨረታ ማስከበሪያ ገንዘብ በዲ.ኤም.ሲ. ኮንስትራክሽን
ኃላ/የተ/የግ/ማህበር ስም በተዘጋጀ C.P.O. ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
5. ተጫራቾች የገዣቸውን ንብረቶች የትራንስፖርት ወጪ የማስጫኛና የማውረጃ ወጪ ጨምሮ በራሳቸው የሚሽፍኑ
ይሆናል።
6. ተጫራቾች ያገለገሉ እቃዎቹን ሊጋቡ የሚችሉበትን ዋጋ በተዘጋጀው የዋጋ ማቅረቢያ ፎርም ላይ በመሙላት ከጨረታ ማስከበሪያ C.P.O. ጋር በማያያዝ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ በማድረግ ማስታወቂያው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ዘወትር በስራ ስዓት እስከ መስከረም 12 ቀን 2019 ዓ/ም ከቀነ- 8:00 ሰዓት ድረስ የድርጅቱ ዋና መስሪያ ቤት በሚገኝበት ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ለቡ መብራት ኃይል አደባባይ ዲ.ኤም.ሲ ሪል እስቴት ህንፃ 10ተኛ ፎቅ ዋና ስራ እሲኪያጅ ቢሮ ለጨረታው በተዘጋጀ ሳጥን ማስገባት ይችላሉ፡፡
7. ጨረታው መስከረም 12 ቀን 2019 ዓ/ም ከቀኑ 8:30 ሰዓት ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት የድርጅቱ ዋና መስሪያ ቤት በሚገኝበት ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ለቡ መብራት ኃይል አደባባይ ዲ.ኤም.ሲ ሪል እስቴት ህንፃ 10ተኛ ፎቅ ዋና ስራ አስኪያጅ ቢሮ ይከፈታል፡፡
8. አንድ ተጫራች ለሁለቱም ወይም ከሁለት ለአንዱ ንብረት መወዳደር ይችላል::
9. ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ጨረታው በሚከፈትበት ቀንና ሰዓት ባይገኙ በሌሉበት ይከፈታል፡፡
10. ተጫራቾች ያሸነፉባቸውን ያገለገሉ እቃዎች ባቀረቡት ነጠላ ዋጋ መሰረት በአጠቃላይ ብዛቱ ተባዝቶ ጠቅላላ ዋጋውን በመክፈል አሸናፊነታቸው በተገለጸላቸው በአስር ቀን ውስጥ ማንሳት ይኖርባቸዋል፡፡ ይህን ሳያደርጉ ቢቀሩ ለጨረታ ማስከበሪያ ያስያዙት ገንዘብ ለድርጅቱ ገቢ ይደረጋል፡፡
11. ድርጅቱ ጨረታውን በከፊል ወይም ሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው::
የዋጋ ማቅረቢያ ፎርም
|
ተ.ቁ |
የንብረቱ አይነት
|
ብዛት በቁጥር
|
ነጠሳ ዋጋ /ከቫት በፌት/
|
ጠቅላላ ዋጋ /ከቫት በፊት/
|
|
1.
|
የሬጅ/Bitumen/በርሜል
|
322
|
|
|
|
2. |
የሲሚንቶ ከረጢት
|
5,000
|
|
|
|
|
ጠቅሳሳ ዋጋ /ከቫት በፌት/
|
|
||
|
ተ.እ.ታ (15%)
|
|
|||
|
ጠቅላላ ዋጋ /ከቫት ጨምሮ/
|
|
|||
12. ተጨማሪ መረጃ በስልክ ሊገኝ ይችላል፡፡
ስልክ 0995028807/0974968888
