Tender Detail

Tender Details

  • Company Ministry of Revenues (የገቢዎች ሚኒስቴር)
  • Address አዲስ አበባ ፡ ኢትዮጵያ, Phone: 011-617-84-90
  • Websitehttp://WWW.MOR.Gov.et
  • Deadline01 Oct 2026, 9:45 AM
  • magazineAddis Zemen
  • Bid Document Priceብር 100.00 (አንድ መቶ)
  • opening dateበዚያን ቀን 4፡00
  • Categories Machinery , Disposal Sale , Vehicle

በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የገቢዎች ሚኒስቴር በታክስ ዕዳ የያዛቸውን የጫማ ማምረቻ ማሽኖች የአምፖል ማምረቻ ማሽኖች የልብስ መስፈያ ማሽኖች፣ የተለያዩ ሞዴል ያላቸው ተሸከርካሪዎችንና የሞተር ሳይክሎችን ለመሸጥ የወጣ የግልጽ ጨረታ ሽያጭ ማስታወቂያ ቁጥር 01/2019


የጨረታ ማስታወቂያ

በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የገቢዎች ሚኒስቴር በታክስ ዕዳ የያዛቸውን የጫማ ማምረቻ ማሽኖች የአምፖል ማምረቻ ማሽኖች የልብስ መስፈያ ማሽኖች፣ የተለያዩ ሞዴል ያላቸው ተሸከርካሪዎችንና የሞተር ሳይክሎችን ለመሸጥ የወጣ የግልጽ ጨረታ ሽያጭ ማስታወቂያ ቁጥር 01/2019

የሚኒስቴር መ/ቤቱ ግብር ከፋዮች የሚጠበቅባቸውን የታክስ ዕዳ በታክስ ህጉ በተፈቀደው የጊዜ ገደብ ባለመከፈላቸው ምክንያት በታክስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 983/2008 አንቀፅ 41 በተሰጠው ስልጣን መሠረት ከሊያንችን ፕላስቲክ ፕሮዳክሽን ማኑፋክቸሪንግ ኃ/የተ/የግ/ማህበር የጫማ ፋብሪካ የተያዘ የጫማ ማምረቻ ማሽን፣ ከኤቢሲ ማኑፋክቸሪንግ ኃ/የተ/የግ/ማህበር የተያዙ የአምፖል ማምረቻ ማሽኖች ከኤሊአላ ጋርመንትና ጨርታ ጨርቅ ኃ/የተ/የግ/ማህበር የተያዘ የልብስ ስፌት ማሽን ሴንጀር የተለያየ ብትን ጨርቅና የተሰፋ ቲሸርት ጃኬት እንዲሁም ጄነሬተር፣ ከእሺ ፈጣን መልዕክት አገልግሎት ኃ/የተ/የግ/ማህበር፣ ከአረብ ኮንስትራክሽን ኃ.የተ.የግ/ማህበር፣ ከምቾት ዳይፐር ማምረቻ ኃ/የተ/የግ/ማህበር የተያዙ የተለያየ ሞዴል ያላቸውን ተሽከርካሪዎችን እና የሞተር ሳይክሎችን ባሉበት ሁኔታ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡

በመሆኑም

  1. በግልፅ ጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልግ ማንኛውም ተጫራች ማንነቱን የሚገልጽ የነዋሪነት መታወቂያ (ፓስፖርት ኮፒ) ከጨረታ ሰነዱ ጋር አያይዞ በኢንቨሎፕ በማሸግ ለግልፅ ጨረታ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርበታል፡፡
  2. ተጫራቾች የጨረታውን ሰነድ ይህ የግልፅ ጨረታ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ዘወትር በስራ ሰዓት ከሰኞ እስከ አርብ እና ቅዳሜ ጠዋት ከ2:00-6:00 ሰዓት ህንፃ መ* 3ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 301 ከግዥና ፋይናንስ አስተዳደር ዳይሬክቶሬት የማይመለስ ብር 100.00 (አንድ መቶ) በመክፈል የጨረታ ሰነዱን ህንፃ "ሀ" 2ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 201 ከታክስ ዕዳ አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ቢሮ መውሰድ ይኖርበታል።
  3. በግልጽ ጨረታ ለመሳተፍ ተጫራቾች ለሚወዳደሩባቸው ንብረቶች የሰጡትን ዋጋ እንድ አስረኛውን ብቻ ለጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና (CPO) በገቢዎች ሚኒስቴር ስም (Ministry of Revenue) በባንክ አሰርተው ማስያዝ ይኖርባቸዋል።
ተ.ቁ የመ/ቤቱ ስም ሰጨረታ የቀረበው የንብረት ዓይነት የንብረቶቹ መመልከቻ ቀን የጨረታው የመዝጊያ እና የመከረቻ ቀንና ሰዓት
1 ገቢዎች ሚኒስቴር የጫማ ማምረቻ ማሽኖች የአምፖል ማምረቻ ማሽኖች የልብስ ስፌት ማሽን የተለያየ ብትን ጨርቆች፣ ጃኬት እንዲሁም ጀነሬተር እና የለያየ ሞዴል ያላቸው ተሸከርካሪዎችና ሞተርሳይክሎች ማስታወቂያው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ 115 ቀናት ማስታውቂያው በጋዜጣ ወጥቶ 15 ቀን ከተጠናቀቀ በኋላ ቀጥሎ ባለው 16ኛ ቀን 3፡45 ተማቶ በዚያን ቀን 4፡00 ሰዓት ይከፈታል፡፡
  1. ተጫራቾች በሚከተለው የጨረታ ቀናት (ስኬጁል) መሰረት ሰነድ በዝተው መጫረት ይችላሉ።
ተ.ቁ የመ/ቤቱ ስም ሰጨረታ የቀረበው የንብረት ዓይነት የንብረቶቹ መመልከቻ ቀን የጨረታው የመዝጊያ እና የመከረቻ ቀንና ሰዓት
1 ገቢዎች ሚኒስቴር የጫማ ማምረቻ ማሽኖች የአምፖል ማምረቻ ማሽኖች የልብስ ስፌት ማሽን የተለያየ ብትን ጨርቆች፣ ጃኬት እንዲሁም ጀነሬተር እና የለያየ ሞዴል ያላቸው ተሸከርካሪዎችና ሞተርሳይክሎች ማስታወቂያው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ 115 ቀናት ማስታውቂያው በጋዜጣ ወጥቶ 15 ቀን ከተጠናቀቀ በኋላ ቀጥሎ ባለው 16ኛ ቀን 3፡45 ተማቶ በዚያን ቀን 4፡00 ሰዓት ይከፈታል፡፡
  1. የጨረታ መከፈቻ ቦታ፡- መገናኛ በሚገኘው በሚኒስቴር መ/ቤቱ የመሰብሰቢያ አዳራሽ ተራቶች ህጋዊ ወኪሎቻቸው ባለቤት ወይም በታዛቢዎች ፊት ይከፈታል ።
  2. የግልፅ ጨረታው መክፈቻና መዝጊያ 16ኛው ቀን የመ/ቤቱ የሥራ ቀን ካልሆነ በቀጣዩ ቀን የግልፅ ጨረታ መክፈቻና መዝጊያ ቀን ይሆናል፤
  3. ለጨረታው አሸናፊ ተጫራቾች ለጨረታው ማስከበሪያ ዋስትና ያስያዙት (CPO) ከሚከፍሉት ዋጋ ጋር አንደ አስፈላጊነቱ የሚታሰብላቸው ሲሆን ለተሸናፊ ተጫራቶች ደግሞ የግልፅ ጨረታ ኮሚቴው መረጃውን አጣርቶ እንደጨረሰ በ5 የስራ ቀናት ውስጥ ተመላሽ ይደረግላቸዋል፡
  4. የተሽከርካሪ ጨረታ ለሚያሸንፉ ተጫራቾች ከስመ ንብረት ዝውውር ጋር ተያያዥነት ያላቸውን ወጪዎች (የቦሎና ሌሎች ተጓዳኝ ወጪዎች) ሻጭን አይመለከትም።
  5. አሸናፊ ተጫራቾች ማሸነፋቸውን በደብዳቤ ከተገለፀላቸው ቀን ጀምሮ ባሉት 15 ቀናት ውስጥ ያሸነፉበትን ጠቅላላ ዋጋ መ/ቤቱ በሚሰጠው አድራሻ ገቢ በማድረግ ያሸነፋበትን ቀንና ሰዓት ሀብት ንብረት መረከብ ይኖርባቸዋል፡፡
  6. ከላይ በተ/ቁ 9 በተገለጹት ቀናት ውስጥ ከፍያውን ገቢ በማድረግ ንብረታቸውን ያልተረከቡ ተጫራቾች የግልፅ ጨረታው ለጨረታ ማስከበሪያ በCPO ያስያዙት የዋሉትና ገንዘብ ለሚኒስቴር መ/ቤቱ ገቢ ሆኖ ንብረቱ እንዳልተሸጠ ተቆጥሮ በቀጣይ በድጋሚ ለሽያጭ ያቀርባል፡፡
  7. ሚኒስቴር መ/ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ የግልፅ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር 011617-84-90 ኮድ 2044 (2045) (2046) የውስጥ መስመር (EXT) 2044 ደውለው መጠየቅ ወይም የተቋሙን ዊብሳይት www.MOR.GOV.et መመልከት ይቻላል፡፡

ገቢዎች ሚኒስቴር

✨ messages.ai_summary
Ethiopia's Ministry of Revenues is selling by open bid machinery seized for tax debt: shoe-making, ampoule-making and garment-sewing machines, fabrics, jackets, a generator, plus various vehicles and motorcycles. Bidders must submit ID and a CPO in the Ministry's name.
Save Tender