ኩባንያችን ኦሮሚያ ኢንሹራንስ አ.ማ የሙሉ ውድመት ካሣ ክፍያ ፈጽሞ የተረከባቸውን ተሽከርካሪዎች እና የተሽከርካሪ አካላት እንዲሁም የተገለገለባቸው የቢሮ መገልገያ ቁሳቁሶች እና የተለያዩ አቃዎች ባሉበት ሁኔታ በጨረታ አወዳድሮ ቅዳሜ ህዳር 06 ቀን 2018 ዓ.ም ለመሸጥ ይፈልጋል።
የጨረታ ማስታወቂያ
ኩባንያችን የሙሉ ውድመት ካሣ ክፍያ ፈጽሞ የተረከባቸውን ተሽከርካሪዎች እና የተሽከርካሪ አካላት እንዲሁም የተገለገለባቸው የቢሮ መገልገያ ቁሳቁሶች እና የተለያዩ አቃዎች ባሉበት ሁኔታ በጨረታ አወዳድሮ ቅዳሜ ህዳር 06 ቀን 2018 ዓ.ም ለመሸጥ ይፈልጋል።
በጨረታው መሳተፍ የሚፈልገ ማንኛውም ተጫራች ተሽከርካሪዎቹ እና ሌሎች ቁሳቁሶች በሚገኙበት ቃሊቲ ሸዋ ዳቦ ጀርባ ሰለሞን ብሎኬት ማምረቻ አጠገብ በሚገኘው የኩባንያችን ሪከቨሪ ቅጥር ገቢ ውስጥ ጥቅምት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ዘወትር በሥራ ሰዓት እስከ ህዳር 05 ቀን 2018 ዓ.ም በመመልከት የሚጫረቱበትን የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 200.00 (ሁለት መቶ) በመክፈል ቦሌ ወሎ ሰፈር ወደ ወንጌላዊት ህንጻ በሚወስደው መንገድ ቴሌ ማሰልጠኛ አለፍ ብሎ ሊዲያ አስናቀ ህንፃ ላይ በሚገኘው ዋና መ/ቤታችን 2ኛ ፎቅ በመግዛት ሰነዱን በሰም በታሸገ ኢንቨሎፕ በማሸግ ለዚህ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ህዳር 04 አና ህዳር 05 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ ቀኑ 11፡00 ድረስ ገቢ በማድረግ መጫረት የምትችሉ መሆኑን አንገልጻለን።
ማሳሰቢያ-
- ጨረታው በኩባንያው ዋና መ/ቤት 3ኛ ፎቅ ላይ በሚገኘው የሥልጠና አዳራሽ ቅዳሜ ህዳር 06 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት ላይ የውስጥ ኦዲት ስገልግሎት እና ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት የሚከፈት ሲሆን፣
- ተጫራቾች በሚያቀርቡት ዋጋ ላይ ተንተርሶ ዋጋ መሥጠት የተከለከለ ነው።
- ተጫራቾች ለተሽከርካሪ የሚጫረቱ ከሆነ ለእያንዳንዱ ተሽከርካሪ የጨረታውን መነሻ ዋጋ 15% ወይም በጨረታ ሰነዱ ላይ በተጠቀሰው መሠረት በባንክ ክፍያ ማስያዣ (CPO) በታሸገ ኢንቨሎፕ ከነዋጋው ማስገባት የሚጠበቅባቸው ሲሆን፣ የተሽከርካሪ አካላት የሚጫረቱ ከሆነ የጨረታ መነሻ ዋጋቸውን መሠረት በማድረግ ኩባንያችን ባስቀመጠው ዝርዝር መሰረት የጨረታ ማስከበሪያ (CPO) ማስያዝ ይኖርበታል።
- ተሽከርካሪዎችን በተመስከተ ከጨረታው በፊት ዕዳ ቢኖር በኩባንያው የሚሸፈን ይሆናል። ሆኖም ግን ከጨረታ በኋላ ያሉትን ማንኛውንም ወጪዎች በሙሉ ገዢው ይሸፍናል።
- የጨረታ አሸናፊዎች ያሸነፉበት ዋጋ ሳይ ተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) 15% (አሥራ አምስት በመቶ) በተጨማሪ ይክፍላሉ።
- አሸናፊዎች የጨረታው ውጤት በኩባንያው የማስታወቂያ ቦርድ እና ድረ ገጽ ላይ የሚገለጽ ሲሆን፣ ውጤቱ ከተገለፀበት ቀን ጀምሮ በአስር (10) ተከታታይ ቀናት ውስጥ አሸናፊዎች ክፍያ ፈጽመው ንብረቶቹን ካስተረከቡ ጨረታው ተሰርዞ ለጨረታው ማስከበሪያ ያስያዙትን ገንዘብ ለኩባንያው ገቢ ይደረጋል።
- የተለያዩ የተሽከርካሪ አካላት እና ቁሳቁሶችን የሚጫረቱ እና አሸናፊ የሚሆኑ በምድብ የተቀመጡትን ቁሳቁሶች ከኩባንያው የሪከቨሪ ግቢ ውስጥ ሙሉ በሙሉ ወጪ የማድረግ ግዴታ አለባቸው።
- ኩባንያው የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ኦሮሚያ ኢንሹራንስ አ.ማ
ዋና መ/ቤት
አድራሻ:- ቦሌ ወሎ ሰፈር ቴሌ ማሰልጠኛ አለፍ ብሎ ሊድያ
አስናቀ ህንፃ
በስልክ ቁጥር 09 11 68 73 41/09 57 08 01 05
ወይም 0115-57-21-48
