የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ፕሮጀክቶች ፖርትፎልዮ ማኔጅመንት ጽ/ቤት የተለያዩ የጽሕፈት መሳሪያዎች /Stationeries/ (በሎት 1) እና የተለያዩ የጽዳት ዕቃዎች (በሎት 2) በዘርፉ ከተሰማሩ ድርጅቶች በጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
ጨረታ ቁጥር EEU-PPM/01/2018(NCB)
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ፕሮጀክቶች ፖርትፎልዮ ማኔጅመንት ጽ/ቤት የተለያዩ የጽሕፈት መሳሪያዎች /Stationeries/ (በሎት 1) እና የተለያዩ የጽዳት ዕቃዎች (በሎት 2) በዘርፉ ከተሰማሩ ድርጅቶች በጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም ከዚህ በታች የተመለከቱትን መስፈርቶችን የሚያሟሉ ድርጅቶች በጨረታ መወዳደር ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የዘመኑን ግብር የከፈሉ መሆናቸውን የሚገልጽ ማስረጃ የሚያቀርቡና በመስኩ ህጋዊ ፍቃድ ያላቸው የታደሰ የንግድ ፈቃድ፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ ለመሆናቸው ማስረጃ ማቅረብ አለባቸው፣
- የጨረታ ሰነዱን ሰኔ 27 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ የማይመለስ ብር 300.00 (ሦስት መቶ ብር) በመkeፈል የኢ.ኤ.አ. ፕሮጀክቶች ፖርትፖልዮ ማኔጅመንት ጽ/ቤት ከካቴድራል መብራት ወደ አራት ኪሎ በሚወስደው መንገድ ከኤንሪኮ ኬክ ቤት 150 ሜትር ርቀት በሚገኘው ማህበራዊ ዋስትና አዲሱ ህንፃ 11ኛ ፎቅ ላይ በመቅረብ መግዛት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች ለሎት 1 የጨረታ ማስከበሪያ ብር 70,000.00 (ሰባ ሺ ብር) እንዲሁም ለሎት 2 የጨረታ ማስከበሪያ ብር 55,000.00 (ሀምሳ አምስት ሺ ብር) በባንከ በተረጋገጠ ሲፒኦ ወይም የዋስትና ጊዜው ከሚያበቃበት ቀን በኋላ 28 ቀን ተጨማሪ ጊዜ ያለውን የባንክ ዋስትና (Bank Guarantee) በኢ.ኤ.አ. አ.አ.ኤ.አ.ፕ ወይም EEU-UEAP ስም ተዘጋጅቶ ከጨረታ ሰነዱ ጋር ማቅረብ አለባቸው።
- ተጫራቾች የሚወዳደሩባቸውን ዋጋ በታሸገ ኤንቨሎፕ በማድረግ ጨረታ ቁጥር EEU-PPM/01/2018 (NCB) የሚል ምልከት በማድረግ እና የሎት ቁጥሩን በመፃፍ ለሎት 1 እስከ ሐምሌ 14 ቀን 2017 ዓ.ም እንዲሁም ለሎት 02 እስከ ሐምሌ 15 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ድረስ በኢ.ኤ.አ. ፕሮጀክቶች ፖርትፎልዮ ማኔጅመንት ጽ/ቤት ከካቴድራል መብራት ወደ አራት ኪሎ በሚወስደው መንገድ ከኤንሪኮ ኬክ ቤት 150 ሜትር ርቀት በሚገኘው ማህበራዊ ዋስትና አዲሱ ህንፃ 11ኛ ፎቅ በመምጣት ለዚሁ ጨረታ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፣
- ጨረታው ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት /ባይገኙም/ ሎት 1 ሐምሌ 14 ቀን 2017 ዓ.ም እንዲሁም ሎት 2 ሐምሌ 15 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 8፡30 ላይ ይከፈታል፣
- ስለጨረታው ዝርዝር መረጃ የጨረታ ሰነዱን ዘወትር በስራ ሰዓት ከሰኞ እስከ አርብ ጧት ከ2፡00-6፡00 ከሰዓት 7፡00-11፡00 እና ቅዳሜ ጧት 2፡00 – 6፡00 ሰዓት መመልከት ይችላሉ ፡፡
- የፕሮግራም ጽ/ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
- ተጫራቾች መረጃ ከፈለጉ በስልከ ቁጥር 0111263159 መደወል ይችላሉ፡፡
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የፕሮጀክት ፖርትፎሊዮ ማኔጅመንት ጽ/ቤት
