በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ የወረዳ 13 ጀ/አ አስተዳደር ጽ/ቤት ስር ላሉት ጽ/ቤቶች 2017 በጀት ዓመት የሚያስፈልጋቸውን እቃዎች ብቃት ያላቸውና በመስኩ የተሰማሩ ተጫራቾችን አወዳድሮ ግዢ መፈጸም ይፈልጋል፡፡
ግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ
የግዢው መለያ ቁጥር ግልጽ ጨረታ 02/17
በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ የወረዳ 13 ጀ/አ አስተዳደር ጽ/ቤት ስር ላሉት ጽ/ቤቶች 2017 በጀት ዓመት የሚያስፈልጋቸውን፡-
ሎት-1 አላቂ የቢሮ እቃዎች 6212
ሎት-2 የጽዳት እቃዎች 6218
ሎት-3 ፈርኒቸር ጥገና 6243
ሎት-4 ቋሚ እቃዎች 6313
ሎት-5 የመስተንግዶ አገልግሎት 6233
ሎት-6 የደንብ ልብስ 6211
ሎት-7 ቋሚ አላቂ እቃዎች 6219
ብቃት ያላቸውና በመስኩ የተሰማሩ ተጫራቾችን አወዳድሮ ግዢ መፈጸም ይፈልጋል፡፡
በዚህም መሰረት
- በጨረታው ለመወዳደር ፍላጎት ያላቸው ተጫራቾች የታደሰ ንግድ ፈቃድ ያላቸው፣ የዘመኑን ግብር የከፈሉ፤ ዮቲን እና
- የቫት ተመዝጋቢ የሆኑእና የምስከር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ
- ተጫራቾች የጨረታው ማስከበሪያ በባንክ የተረጋገጠ ሲፒኦ ብር ለሎት1 ብር 10,000 (አስር ሺህ ብር ብቻ) ለሎት2 ብር 7,000 (ሰባት ሺህ ብር ብቻ) ለሎት3 ብር 7,000.00 (ሰባት ሺህ ብር ብቻ) ለሎት4 ብር16,000 (አስራ ስድስት ሺህ ብር ብቻ) ለሎት5 ብር 5,000.00 (አምስት ሺህ ብር ብቻ) ለሎት6 ብር 6,000.00(ስድስት ሺህ ብር ብቻ) ለሎት7 ብር 4,000.00 (አራት ሺህ ብር ብቻ) በን/ስ/ላ/ክ/ከ ወረዳ 13 ጀ/ ፋይናንስ ጽ/ቤት ስም ተዘጋጅቶ ከጨረታው ሰነዳቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው.
- ተጫራቾች ጨረታው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት እለት ጀምሮ በተከታታይ 10 የስራ ቀናት የማይመለስ ብር 200.00 (ሁለት መቶ ብር ብቻ) በመክፈል በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወ/13/ጀ/አ ፋይናንስ ጽ/ቤትጀሞአንደኛ በር በሚገኘው ሳባህንጻ 6ተኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 601 ላይ በመምጣት የጨረታውን ሰነድ መግዛት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የመጫረቻ ሰነዳቸውን በታሸገ ኤንቨሎፕ ማስታወቂያው ከወጣበት እለትጀምሮ ለተከታታይ 10 የስራ ቀናት በፋይናንስ ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 601 በመምጣት ለጨረታ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
- ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊወኪሎቻቸው በተገኙበት በአስረኛው ቀን በ11፡00 ሰዓት ታሽጎ በ11ኛው ቀን በ3፡00 ሰዓት በወረዳው ፋይናንስ ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 601 ይከፈታል፡፡ የመክፈቻ ቀኑ ቅዳሜና እሁድ ወይም የበአል ቀን ከሆነ በሚቀጥለው የስራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓትና ቦታ ታሽጎ ይከፈታል።
- ተጫራቾች የጨረታ ሳጥን ከመከፈቱ በፊት ለተወዳደሩባቸው ሎት1፤ ሎት2፤ ሎት4፣ ሎት5፤ ሎት6 እና ሎት7 ናሙና ማቅረብ የሚኖርባቸው ሲሆን በቀረበው የፍላጎት መግለጫ መሰረት የተሟላ ፍላጎት መግለጫ ማዘጋጀትና ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡ እንዲሁም ለሎት3 የብቃት ማረጋገጫ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች የሚወዳደሩባቸውን እቃዎች ለኢያንዳንዱ ከቫት በፊት እና ከቫትጋር ያለውን ዋጋ ማስቀመጥ ይጠበቅባቸዋል፡፡
- የዘገየ ጨረታ እና በጨረታ መክፈቻ ላይ ያልተነበበ ጨረታ ተቀባይነት የለውም፡፡
- አሸናፊ ተጫራቾች ያሸነፉባቸውን እቃዎች በራሳቸው ትራንስፖርት የግዢ ፈጻሚው መስሪያ ቤት ግምጃቤት ድረስ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡
- መስሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
በተጨማሪ በማብራሪያ ጥያቄ
አድራሻ ጀሞ አንደኛ በር ሳባ ህንፃ 6ተኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 601
ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 13 ፋይናንስ ጽ/ቤት
