በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የፕሮጀከቶች ፖርትፎሊዮ ማኔጅመንት ስራ አስፈጻሚ የፅዳት እቃ በጨረታ አወዳድሮ ግዥ መፈጸም ይፈልጋል ።
በድጋሚ የወጣ የጨረታ ማስታወቂያ
ጨረታ ቁጥር EU-PPM /11/2017 (NCB)
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የፕሮጀከቶች ፖርትፎሊዮ ማኔጅመንት ስራ አስፈጻሚ የፅዳት እቃ በጨረታ አወዳድሮ ግዥ መፈጸም ይፈልጋል ። ስለሆነም ከዚህ በታች የተመለከቱትን መስፈርቶችን የሚያሟሉ ድርጅቶች በጨረታ መወዳደር ይችላሉ ::
- ተጫራቾች የዘመኑን ግብር የከፈሉ መሆናቸውን የሚገልጽ ማስረጃ የሚያቀርቡና በስሙ ህጋዊ ፍቃድ ያላቸው የታደሰ የንግድ ፈቃድ እና የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ በኢፌዲሪ የመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ድህረ ገጽ በአቅራቢዎች ዝርዝር የተመዘገቡ ለመሆናቸው ማስረጃ ማቅረብ አለባቸው፣
- የጨረታ ሰነዱን በጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ የማይመለስ ብር 300.00 (ሶስት መቶ ብር) በመክፈል የኢ.ኤ.አ ፕሮጀክቶች ፖርትፎልዮ ማኔጅመንት ጽ/ቤት ከካቴድራል መብራት ወደ አራት ኪሎ በሚወስደው መንገድ ከኤንሪኮ ኬክ ቤት 150 ሜትር ርቀት በሚገኘው ዋስትና የንግድ ማእከል አዲሱ ህንጻ ላይ 11ኛ ፎቅ በመቅረብ መግዛት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ ብር 15,000 (አስራ አምስት ሺ ብር) በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ ወይም የባንከ ዋስትና (Bank Guarantee) ጨረታው ፀንቶ ከሚያበቃበት ቀን በኃላ 28 ቀን ተጨማሪ ጊዜ ያለው በእ.ኤ.አ. ፕሮጀክት ፖርትፖልዮ ማነጅመንት ወይም EEU-PPM ስም ተዘጋጅቶ ከጨረታ ሰነዱ ጋር በሰንጠረዥ በተገለጽው ብር መጠን ማቅረብ አለባቸው::
- ተጫራቾች የሚወዳደሩባቸውን ዋጋ በታሸገ ኤንቨሎኘ በማድረግ ጨረታ ቁጥር EU- PPM/11/2017 (NCB) የሚል ምልከት በማድረግ እስከ ህዳር 06 ቀን 2017 ዓ.ም እስከ ቀኑ 8፡00 ሰዓት ድረስ በኢ.ኤ.አ ፕሮጀክቶች ፖርትፎልዮ ማኔጅመንት ጽ/ቤት ዋስትና ንግድ ማዕከል 11ኛ ፎቅ በመምጣት ለዚሁ ጨረታ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፣
- ጨረታው ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት /ባይገኙም/ ህዳር 06 ቀን 2017 ከቀኑ 8፡30 ላይ ይከፈታል፣
- ስለጨረታው ዝርዝር መረጃ የጨረታ ሰነዱን ዘወትር ከሰኞ እስከ አርብ ጠዋት 2፡00 እና ከሰአት በኋላ 7፡00 – 11፡00 እንዲሁም ቅዳሜ 2፡00 – 6፡00 ይመልከቱ ::
- የፕሮጀክቶች ጽ/ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው ::
- ተጫራቾች መረጃ ከፈለጉ በስልክ ቁጥር 011-1-26-31-53 መደወል ይችላሉ፡፡
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የፕሮጀክቶች ፖርትፎሊዮ ማኔጅመንት ጽ/ቤት
