ቡሉኮ ጨርቃ ጨርቅ አክሲዮን ማህበር ከ2018 በጀት ዓመት ጀምሮ ለሶስት ተከታታይ (እ.ኢ.አ የ2018 የ2019 እና የ2020) የበጀት ዓመታት የሂሳብ ምርመራ (ኦዲተር) በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ውል በመግባት ለማሠራት ይፈልጋል።
የግልፅ ጨረታ ማስታወቂያ
በግዥ መለያ ቁጥር (ብ.ግ.ጨ.ቁ BTSC/NCB/Serv/09/2018)
ቡሉኮ ጨርቃ ጨርቅ አክሲዮን ማህበር በኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥትና በግል ባለሃብቶች ሽርክና የተቋቋመ የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት የልማት ድርጅት ነዉ። ድርጅታችን ከ 2018 በጀት ዓመት ጀምሮ ለሶስት ተከታታይ (እ.ኢ.አ የ2018 የ2019 እና የ2020) የበጀት ዓመታት የሂሳብ ምርመራ (ኦዲተር) በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ውል በመግባት ለማሠራት ይፈልጋል።
በዚህም መሠረት በግልፅ ጨረታው ላይ የሚሳተፉ ተጫራቾች ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መረጃዎች ማሟላትና ማቅረብ አለባቸው።
1. ከሚመለከተው አካል በዘርፉ የሙያ ብቃት ማረጋገጫ የወሰደና እና የታደሰ፤
2. የታደሰ ንግድ ፈቃድና የምዝገባ ምስክር ወረቀት፣
3. የግብር ከፋይ የምዝገባ ሠርተፍኬት፣
4. የተጨማሪ እሴት ታክስ የምዝገባ ሠርተፍኬት፤
5. የጨረታ ማስከበሪያ ብር 20,000.00 (ሃያ ሺህ ብር) በባንከ የተረጋገጠ በሲፒኦ ወይም የባንክ ያለገደብ ዋስትና (ጋራንቲ) ማቅረብ የሚችል።
6. በጨረታው መሳተፍ የሚፈልጉ የጨረታውን ሠነድ የማይመለስ ብር 1,000.00 (አንድ ሺህ ብር) በመክፈል በሸገር ከተማ ፉሪ ክ/ከተማ (ኬንተሪ ወደ ቡታጅራ በሚወስደው መንገድ 1.3 ኪ/ሜ ላይ) በድርጅቱ ቅጥር ግቢ የግዥና አቅርቦት መምሪያ ቢሮ በመቅረብ የጨረታ ሰነዱን ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ዘወትርበስራ ሰዓት ከጠዋቱ 3፡00 እስከ 6፡00 ከሰዓት በኋላ ከ7፡30 እስከ 10፡30 ሰዓት ቅዳሜ ከጠዋቱ 3፡00 እስከ 6፡00 ሰዓት መግዛት ይቻላል።
7. ጨረታው ግንቦት 11 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡15 ሰዓት ተዘግቶ በዕለቱ ተጫራቾች በተገኙበት 4፡30 ሰዓት ላይ ይከፈታል።
8. ለተጨማሪ ማብራሪያ በስልክ ቁጥር 0996-672-951 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ።
9. ድርጅቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
አድራሻ፡
ቡሉኮ ጨርቃ ጨርቅ አክሲዮን ማህበር
ኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት ሸገር ከተማ ፣ ፉሪ ክ/ከተማ (ከኬንትሪ ወደ ቡታጅራ መንገድ 1.3 h..%)
ቡሉኮ ጨርቃ ጨርቅ አክሲዮን ማህበር
