የቡሉኮ ጨርቃጨርቅ አክሲዮን ማህበር ለድርጀቱ አገልግሎት የሚውሉ የፅሕፈትና ቢሮ መገልገያ ዕቃዎችን እና የፅዳት ዕቃዎችን በአንድ ዓመት (Framework) ውል በመግዛት በሀገር ውስጥ ግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
የግልፅ ጨረታ ማስታወቂያ
በግዥ መለያ ቁጥር BTSC/NCB/G/09/2018
የቡሉኮ ጨርቃጨርቅ አክሲዮን ማህበር ለድርጀቱ አገልግሎት የሚውሉ የፅሕፈትና ቢሮ መገልገያ ዕቃዎችን እና የፅዳት ዕቃዎችን በአንድ ዓመት (Framework) ውል በመግዛት፡- ሕጋዊ ሰነዶችን ማለትም
- ሀ. በዘመኑ የታደሰ ንግድ ፈቃድ
- ለ. የንግድ ምዝገባ ምስክር ወረቀት
- ሐ. ቲን ቁጥር
- መ. የቫት ተመዝጋቢነት ሰርተፊኬት
- ሠ. ከገቢዎች ባለስልጣን የዘመኑን ግብር መክፈሉን በጨረታ ለመወዳደር እንዲችል ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት ያለው እና የሥራ ልምድ ካላቸው ድርጅቶች በሀገር ውስጥ ግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡ በዚሁ መሰረት
- ተጫራቾች የጨረታ ሠነድ የማይመለስ ብር 1,000.00 (አንድ ሺህ) በመክፈል ሸገር ከተማ ፉሪ ክ/ከተማ (ከዓለም ወደ ቡታጅራ በሚወስደው መንገድ 1.3 ኪሜ ላይ) የቀድሞው አይካ አዲስ ጨርቃጨርቅ ፋብሪካ ቅጥር ግቢ የድርጅቱ የግዥና አቅርቦት መምሪያ በመቅረብ የጨረታ ሠነዱ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ዘወትር በስራ ሰዓት ከጠዋቱ 3፡00 - 6፡00 ከሰዓት በኋላ ከ7:30 - 10:30 ሰዓት መግዛት ይችላሉ።
- ተጫራች የጨረታ ማስከበሪያ ከጨረታ ሠነዱ ጋር በባንክ የተረጋገጠ በሲፒኦ ወይም ያልተገደበ የባንክ ዋስትና ለሎት አንድ ብር 20,000.00 (ሃያ ሺህ) እንዲሁም ለሎት ሁለት ብር 20,000.00 (ሃያ ሺህ) ማስያዝ አለበት፡፡
- ጨረታው ታህሳስ 06 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 5፡00 ሰዓት ተዘግቶ በዕለቱ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው እና ታዛቢዎች በተገኙበት ከጠዋቱ 5፡10 ሰዓት ላይ ይከፈታል፡፡
- የጨረታው የመክፈቻ ቀን ከአቅም በላይ ሁኔታ ሲገጥም ወይም የበዓል ቀን ላይ ከዋለ በሚቀጥለው የሥራ ቀን ከላይ በተጠቀሰው ሰዓት ይከፈታል፡፡
- ለተጨማሪ ማብራሪያ በስልክ ቁጥር 0996-672-951 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡
- ድርጅቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
አድራሻ፡ ቡሉኮ ጨርቃ ጨርቅ አክሲዮን ማህበር
ሸገር ከተማ ፣ ፉሪ ክ/ከተማ (ከዓለም ገና ወደ ቡታጅራ መንገድ 1.3 ኪ.ሜ) የቀድሞው አይካ አዲስ ጨርቃጨርቅ
የቡሉኮ ጨርቃጨርቅ አክሲዮን ማህበር
