የደ/ብርሃን እንጨት ማቀነባበሪያ ኃ/የተ/የግል ማህበር ሰኘላይውድ እና ቨነር ማምረቻ ማሽኖች መለዋወጫ የሚሆን ሮለር ብሊድ ምላጭ ሀይድሮሊክ ፓምፕ የፎርክ ሊፍቶች ኢንጅን መለዋወጫ እንዲሁም የተለያዩ መለዋወጫዎች በዘርፉ ከተሰማሩ ድርጅቶች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል
ግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ
ካምፓኒያችን የደ/ብርሃን እንጨት ማቀነባበሪያ ኃ/የተ/የግል ማህበር ሰኘላይውድ እና ቨነር ማምረቻ ማሽኖች መለዋወጫ የሚሆን ሮለር ብሊድ ምላጭ ሀይድሮሊክ ፓምፕ የፎርክ ሊፍቶች ኢንጅን መለዋወጫ እንዲሁም የተለያዩ መለዋወጫዎች በዘርፉ ከተሰማሩ ድርጅቶች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
በዚህ መሰረት
1. በዘርፉ የተሰማራና የንግድ ስራ ፈታዱን ያሳደሰ
2. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር /ቲን ነምበር, ያላቸው
3. የቫት ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችል፣
4. ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ ከላይ ከተራ ቁጥር 1-3 የተጠቀሱትና ሌሎች የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው።
5. ተጫራቾች ለዕቃዎቹ የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና /ቢድ ቦንድ/ 30,000 (ሰላሳ ሺህ ብር) በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትእዛዝ CPO ማስያዝ አለባቸው።
6. ተጫራቾች በሚያተርቡት ሰነድ ላይ ስማቸውን ፊርማቸውንና አድራሻቸውን ማስፈርና የድርጅቱን ማህተም ማድረግ አለባቸው።
7. በመጫረቻ ሰነዱ ላይ ምንም አይነት ስርዝ ድልዝ መኖር የለበትም ካለም አንድ ሰረዝ በማድረግ ፊርማቸውን ማስቀመጥ ይኖርባቸዋል።
8. ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሰነዱን በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ በካምፓኒው የፋይናንስ ቢሮ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ለተከታታይ 16 ቀናት ዘወትር በስራ ሰዓት ይህ ጨረታ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ድረስ የጨረታውን ሰነድ ገቢ ማድረግ ይችላሉ።
9. ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በ16ኛው ቀን/ጨረታው በተዘጋበት ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ላይ ታሽጎ 4፡30 ሰዓት ላይ በካምፓኒው የፋይናንስ ቢሮ ውስጥ በይፋ ይከፈታል። ተጫራቾች ባይገኙም ከመከፈት እይታገድም።
10. የመክፈቻ ቀኑ እሁድ ወይም የህዝብ በዓላት ላይ ከዋለ በሚቀጥለው ቀን ከላይ በተገለጸው ሰዓት ይሆናል።
11. አሸናፊ ሆኖ የተመረጠው ተጫራች የውል ማስከበሪያ የሚሆን ገንዘብ በሲፒኦ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና የአሸነፈበትን ጠቅላላ ዋጋ 10% ማስያዝ አለበት ።
12. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን በማይመለስ ብር 200.00 /ሁለት መቶ ብር/ በመክፈል ከካምፓኒው የፋይናንስ ቢሮ መውሰድ ይችላሉ።
13. ከተጠቀሰው ብዛት ወይም መጠን በታች ቀንሶ መጫረት ውጤት ላያስገኝ ይችላል።
14. አትራቢ ድርጅቱ የማስጫኛ እና የማስወረጃ እንዲሁም ሌሎች ወጪዎችን ሸፍኖ ንብረቱን ለካምፓኒው ንብረት ክፍል ያስረክባል።
15. የሁሉም እቃዎች ዝርዝር መግለጫ በጨረታ ሰነዱ ላይ ይገኛል።
16. ካምፓኒው የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር፡- 011 637 58 03 ደውለው ይጠይቁ
የደ/ብርሃን እንጨት ማቀነባበሪያ ኃ/የተ/የግል ማህበር
