በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ ራስ ደስታ ዳምጠው ሆስፒታል ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን አቅርቦቶች ለ2018 በጀት ዓመት ግዥ መፈፀም ይፈልጋል።
የእቃ ግዥ ጨረታ፤ ጨረታ ቁጥር ብ/ግ/ጨ/ቁ/04/2018
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ ራስ ደስታ ዳምጠው ሆስፒታል ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን አቅርቦቶች ለ2018 በጀት ዓመት ግዥ መፈፀም ይፈልጋል፡-
· ሎት 1፡- የመኪና ጎማ ግዥ
በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም በጨረታው ለመሣተፍ የሚፈልግ ተጫራች፡-
1. በዘርፉ ህጋዊ ንግድ ፍቃድ ያለውና የዘመኑን ግብር ከፍሎ ፍቃዱን ያደሰ፤
2. የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ፣ የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር ያለውና፣ ማስረጃ ማቅረብ የሚችል፤
3. የአቅራቢነት ማስረጃ ያለው፤
4. ከገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን ስለ ግብር አከፋፈል የሚሰጥ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፤ መሆን ይኖርባቸዋል፡፡
5. ማንኛውም ተጫራች በጨረታው ለመሣተፍ የጨረታ ማስከበሪያ
ሎት 1- የመኪና ጎማ ግዥ 10,000.00 ብር
በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ (CPO)፣ ወይም ጥሬ ገንዘብ ብቻ ማስያዝ አለባቸው።
6. አሸናፊ ተጫራቾች ያለምንም የአቅርቦት ችግር አስተማማኝ የሆነ የእቃ ክምችት (የራሱ ስቶክ) ያለውና፤ እቃዎቹን በራሱ ማጓጓዣ (ወጪ) እስከ ሆስፒታሉ እቃ ግምጃ ቤት ድረስ አምጥቶ እና በራሱ ወጪ አውርዶ ማስረከብ ተጫራቾች የሚወዳደሩበትን የጨረታ ሰነድ ሙሉ መረጃቸውን እና፧ ኮፒ በመያዝ የጨረታ ሰነድ ለመግዛት መምጣት ይኖርባቸዋል፤ የማይመለስ ብር 200.00 /ሁለት መቶ ብር/ በመክፈል ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ10 (አስር) ተከታታይ የስራ ቀናት ከጠዋት 2፡30 እስከ 10፡00 ሰዓት በሆስፒታሉ ግዥ ዳይሬክቶሬት ቢሮ ያ ቁጥር አዲስ (በመኪና መግቢያ በር ገብቶ ወደ ግራ እጥፍ ብለው) በመቅረብ መውሰድ ይችላሉ፡፡
7. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዳቸው ዋናውንና ኮፒውን በተናጠል በታሸገ ኢንቬሎፕ የሎት ቁጥሩ ሰነድ ሲገዙ የተሰጣቸው መለያ ኮድ ፅፈው፣ የድርጅታቸው ህጋዊ ማህተም መተው፤ ማቅረብ ይኖርባቸዋል። ጨረታቸው አንድ (1) ኢንቨሎፕ ነው፡፡ ኦርጅናል እና ኮፒ ለይተው ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
8. ጨረታው 10 ቀናት የአየር ላይ ቆይታውን እንዳጠናቀቀ በ11ኛው ቀን ጠዋት 3፡00 ሰዓት ተዘግቶ በእለቱ ጠዋት 4፡00 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡ እለቱ በዓል ወይም ቅዳሜና እሁድ ከሆነ በቀጣዩ የሥራ ቀን በተመሣሣይ ሰዓት ጨረታው ይከፈታል፡፡
9. ተጫራቾች የመወዳደሪያ ዋጋቸው ሆስፒታላችን በሰጠው መሙያ ቅጽ ብቻ መሙላት ይኖርባቸዋል፤ ማንኛዉም ስርዝ ድልዝ፣ ማህተም ያልተደረገበት የቀረበ ዋጋ፣ በሆስፒታሉ ዋጋመሙያ ቅጽ ያልተሞላ ዋጋ ተቀባይነት የለውም፡፡ ከጨረታው ውጭ ይደረጋል፡፡
10. ሆስፒታሉ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊል ወይም ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው።
አድራሻ፡- በአራዳ ጊዮርጊስ ቤ/ክ ወደ አስኮ ሚወስደው መንገድ ከዮሐንስ ቤ/ክ 500 ሜትር አለፍ ብሎ እንገኛለን፡፡
ለተጨማሪ ማብራሪያ
አድራሻ፡- ከፒያሳ ወደ አስኮ በሚወስደው መንገድ ከዮሐንስ ቤ/ክ 500 ሜትር አለፍ ብሎ እንገኛለን፡፡
ለተጨማሪ ማብራሪያ
ስልክ ቁጥር፡- 0111112056 ደውሎ መጠየቅ ይቻላል፡፡
ራስ ደስታ ዳምጠው ሆስፒታል
