በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 10 አስተዳደር የተለያዩ መጠን ያላቸው ቆርቆሮዎች በግልጽ ጨረታ ቁጥር 01/2018 አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 10 አስተዳደር የተለያዩ መጠን ያላቸው ቆርቆሮዎች በግልጽ ጨረታ ቁጥር 01/2018 አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡ በዚህም መሰረት
- ተጫራቾች ለጨረታው ዋስትና ያስያዙት ሲፒኦ የጨረታው ውጤት በተገለጸ በ3 ቀናት ውስጥ ተመላሽ ይደረግላቸዋል፡፡
- ተጫራቾች ጨረታው ከመዘጋቱ ከ3 ቀናት ቀደም ብለው ዘወትር በስራ ቀናት ከጠዋቱ 3፡00 እስከ 5፡00 ከሰዓት 8፡30 እስከ 10፡30 ብቻ በመገኘት መጎብኘት ይችላሉ፡፡
- የጨረታው ማስከበሪያ 2% ማለትም 5,000.00 (አምስት ሺህ ብር ብቻ) ሲፒኦ A/K/K/K/W/10/FA/TSE/BET በሚል ሲፒኦ ማስያዝ አለባቸው። ከጨረታው ማስከበሪያ መጠን ወይንም ብር አስበልጦም ሆነ አሳንሶ ሲፒኦ ማሰራት ከውድድር ውጭ ያደርጋል፡፡
- የጨረታውን ሰነድ የማይመለስ ብር 300.00 (ሶስት መቶ) መግዛት ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች የመወዳደሪያ ሰነዳችሁን በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ በማድረግ 1 ኦርጅናል እና ኮፒ በተገለጸው አድራሻ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
- ጨረታው ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ተጫራቾች ወይንም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በ11ኛው የስራ ቀን ከጠዋቱ 3፡00 ተዘግቶ በ11ኛው ቀን ከጠዋቱ 3፡30 በወረዳው ንብረት ክፍል ቢሮ ውስጥ ይከፈታል፡፡ ሆኖም የመክፈቻ ቀኑ ቅዳሜና እሁድ ወይንም የበዓል ቀን ከዋለ በሚቀጥለው የስራ ቀን ይሆናል፡፡ እንዲሁም ተጫራቹ በራሱ ምርጫ ጨረታው በሚከፈትበት ቀን ሳይገኝ ቢቀር የጨረታው መከፈትን አያስተጓጉለውም፡፡
- ተጫራቾች ንብረቱን በራሳቸው ወጪ ንብረቱን ያነሳሉ፡፡
- አሸናፊው ድርጅት ማሸነፉን መ/ቤቱ ካሳወቀበት ቀን በኋላ ባሉት 3 የስራ ቀናት ውስጥ ሙሉ ክፍያውን ከፍለው ንብረቱን ማንሳት ይኖርበታል፡፡ በተጠቀሰው ቀን የማያነሳ ከሆነ ወረዳው ስለንብረቱ ተጠያቂ አይሆንም፣ አሸናፊው የሚለየው በጥቅል ለተመደበው ቆርቆሮ ከፍተኛ ዋጋ ያቀረበ አሸናፊ ይሆናል፡፡ በተጨማሪም መነሻ ዋጋ ሞልቶ ያላቀረብ (ባዶ ሰነድ ብቻ ያስገባ) ተጫራች ከጨረታው ይሰረዛል፡፡
- የሚያቀርቡት ሰነድ ስርዝ ድልዝ ካለው ተቀባይነት የሌለው ሲሆን በመወዳደሪያ ሰነዱ ላይ ካለ የድርጅቱ ማህተም ወይንም ፊርማ ሊኖረው ይገባል፡፡
- ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
- ለተጨማሪ ማብራሪያ የንብረት ስራ ሂደቱን መጠየቅ ይቻላል፡፡
አድራሻ፡- አዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 10 አስተዳደር ግቢ ውስጥ ሲሆን ልዩ ቦታው ኮልፌ አጠና ተራ ከታክሲ ተራው ከፍ ብሎ ስልክ 011-273-95-86 መደወል ይቻላል፡፡
በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 10 አስተዳደር ፋይናንስ ጽ/ቤት
