በቂርቶሰ ክፍለ ከተማ አስቶዳጀር ስር የሚገኘው የመሸለኪያ ጤና ጣቢያ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን የተለያዩ እቃዎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡
ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ መበያ ቁጥር - 01/2019
በቂርቶሰ ክፍለ ከተማ አስቶዳጀር ስር የሚገኘው የመሸለኪያ ጤና ጣቢያ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን የተለያዩ እቃዎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡
| የሎት ቁጥር | የአገልግሎት አይነት | የሚያሲዙት የገንዘብ መጠን በ cpo | የሎት ቁጥር | የአገልግሎት አይነት | የሚያሲዙት የገንዘብ መጠን በ cpo |
| ሎት 1 | መድሃኒት እና የላብራቶሪ አደንት | 30,000 | ሎት 8 | የተለያዩ ህትመቶች እና የሰራተኛ መታወቂያ ባጅ | 15,000 |
| ሎት 2 | የህክምና መገልገያ ቋሚ እቃ | 30,000 | ሎት9 | የካልብሬሽን ሰርቪስ አገልግሎት | 10,000 |
| ሎት 3 | የስራ መገልገያ የደንብ ልብስ ስፌት | 20,000 | ሎት10 | የጤና ጣቢያው አጠቃላይ የህንጻ እድሳት ስራ | 30,000 |
| ሎት 4 | የጽህፈት መሳሪያ እና አላቂ የጽዳት እቃዎች ግዥ | 20,000 | ሎት11 | የጀነሬተርና የላውንደሪ ማሽን ጥገና | 15,000 |
| ሎት 5 | የቢሮ መገልገያ ቋሚ እቃ እና ኤሌክትሮኒክስ እቃዎች ግዥ | 30,000 | ሎት12 | የ CPD አሰልጣኝ ባለሙያ | 10,000 |
| ሎት 6 | ልዩ ልዩ መሳሪያዎች ግዥ | 15,000 | ሎት13 | የኮምፒውተር ፣የላፕተፐፕ፣የፎቶኮፒ ፣ፐሪንተር ጥገና | 10,000 |
| ሎት 7 | የላብራቶሪ ህክምና መሪያዎች ጥገና | 10,000 | ሎት14 | የሰራተኛ ካፍቴሪያ አገልግሎት እና የምግብና የመጠጥ አቅርቦት | 30,000 |
በጨረታ ለመሳተፍ የሚፈልጉ ተጫራቾች የሚከተሉትን መስፈርቶች ማማላት ይጠበቅባቸዋል።
ተጫራቾች በዘርፉ የተሰማሩበትን የታደሰ ንግድ ፍቃድ፣ የታክስ ግዴታውን የሚያመላክቱ የቫት ተመዝጋቢ ማስረጃ፣ የቫት ተመዝጋቢ መሆናቸውን የሚገልጽ ማስረጃ እና ለአነስተኛ እና ጥቃቅን ተቋማት ለሚወዳደሩበት ዘርፍ የድጋፍ ደብዳቤ ማስረጃ በግልጽ የሚታይ ፎቶ ኮፒ ማቅረብ አለባቸው፡፡
እያንዳንዱ ተጫራች የሚወዳደሩበትን እቃ ዋጋ እስከነ ቫቱ መሙላት ይኖርባቸዋል፡፡
እያንዳንዱ የጨረታ ሰነድ የማይመለስ 200 (ሁለት መቶ ብር) በመግዛት በትክክል በመሙላትና በታሸገ ፖስታ ወይም ኢንቬሎፕ በማድረግ የጨረታውን ሰነድ ዋናውን እና ፎቶ ኮፒውን በተናጥል አሸገው የድርጅታችሁን ማህተም በማድረግ በመሸለኪያ ጤና ጣቢያ የግዥ ክፍል በር ላይ በሚገኘው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
የጨረታው ማስከበሪያ አሸናፊዎች ተለይተው ውል አስኪፈፀም ድረስ አገደተያያዘ ይቆያል፡፡
ተጫራቾች አሸናፊ መሆናቸው ከተገለፀላቸው ቀን ጀምሮ ከ7 ቀን በኋላ10%የውል ማስከበሪያ (CPO) ማስያዝ ይኖርባቸዋል።
የጨረታ ሳጥን ከታሸገ በኋላ የሚደርስ ማንኛውም ሰነድ ሳይከፈት ለተጫራቹ ይመለሳል፡፡
መስሪያ ቤቱ የጨረታውን 30% መጨመርና መቀነስ ይችላል።
የጨረታው አሸናፊ ያሸነፈውን እቃ በራሱ የትራንስፖርት ወጪ ጤና ጣቢያው ገብቶ ከፍሎ ድረስ ማቅረብ ይኖርበታል፡፡
ጨረታው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን አንስቶ 10 ተከታታይ የስራ ቀናት አየር ላይ የሚቆይ ሲሆን በመጨረሻው ቀን በ 4፡00 ሰዓት ላይ ታሽጎ በዚያኑ ቀን ከጠዋቱ 4:00 ቢሮ ቁጥር 38 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡
በመጨረሻው ቀን በአል ወይም ዝግ ከሆነ በቀጣዩ የስራ ቀን ጨረታው የሚከፈት ይሆናል፡፡
የጨረታው ሰነድ በመሸለኪያ ጤና ጣቢያ ቢሮ ቁጥር 07 ረዳት ፋይናንስ ኦፊሰር ቢሮ ቀርበው መግዛት ይችላሉ፡፡
ተጫራቾች የሚያቀርቧቸው እቃዎች ጤና ጣቢያው ባዘጋጀው እስፔክስፊኬሽን መሰረት ሲሆነ ለሁሉም እቃዎች ጨረታው ከመከፈቱ በፊት ናሙና ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
መስሪያ ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው ።
አድራሻ ፡-ደብረዘይት መንገድ ቴሌ ጋራዥ ፊት ለፊት ወደ ውስጥ ገባ ብሎ - ማሳሰቢያው ይህ ሰነድ ሙሉ በሙሉ ወይም በክፍል 1 እና 7 ውጭ ያሉት ገጾች ኮፒ በማድረግ የሚጠይቀውን መጠይቅ በመሙላት እያንዳንዱ ገጽ ላይ በመፈፈረም ፣የድርጅታችሁን ማህተም በማድረግ መመለስ አለበት ማሳሰቢያው ተግባራዊ ካልሆነ የሚቀርበው ጐደሎ ሰነድ ተቀባይነት አይኖረውም።
ለተጨማሪ መረጃ፡ ግዥ ክፍል በስልክ ቁጥር 011 4 70 08 10 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ።
የመሻለኪያ ጤና ጣቢያ
