Tender Detail

Tender Details


ኢትዮ ቴሌኮም በደቡብ ደቡብ ምዕራብ ሪጅን በአርባምንጭ ከተማ ላሰራው ህንጻ ብቁ የሆኑ ተጫራቾችን በግልጽ በጨረታ ቁጥር 4287194 አወዳድሮ የግንባታ ኤሌክትሪክ ዕቃ አቅርቦት ሥራ ለማሰራት ይፈልጋል።


ለመጀመሪያ ጊዜ የወጣ የግንባታ ኤሌክትሪክ ዕቃ አቅርቦት ሥራ ጨረታ ማስታወቂያ

ኢትዮ ቴሌኮም በደቡብ ደቡብ ምዕራብ ሪጅን በአርባምንጭ ከተማ ላሰራው ህንጻ ብቁ የሆኑ ተጫራቾችን በግልጽ በጨረታ ቁጥር 4287194 አወዳድሮ የግንባታ ኤሌክትሪክ ዕቃ አቅርቦት ሥራ ለማሰራት ይፈልጋል።

በመሆኑም ከታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የምታሟሉ ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ 31 ተከታታይ ቀናት ማለትም (ከቀን 03/13/2018 ዓ.ም እስከ 28/01/2019 ዓ/ም) የጨረታ ሰነዱን በኢትዮ ቴሌኮም ዌብ ሳይት ላይ ማግኘት ይችላሉ። ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በቀን 28/01/2019 ዓ.ም ከሰዓት በ9፡00 ሰዓት ተዘግቶ ቀን 29/01/2019 ዓ/ም በ 4:00 ጠዋት በኦንላይን ይከፈታል።

የብቁነት መስፈርቶች (A, Eligibility Requirements)

  1. የጨረታ ማስከበሪያ 50,000.00 (ሃምሳ ሺህ ብር ብቻ) በባንክ የተረጋገጠ ሲፒኦ ማቅረብ (Availability of Bid Security, 50,000.00 ETB)
  2. የጨረታ ሰነድ ላይ ለመፈረም የሚያስችል የውክልና (Availability of Letter of Authorization to sign the bid offers;)
  3. የተጫራቾች በስነ ምግባር ደንቦች የመገዛት ቃል ኪዳን ሰነድ/ቅጽ (Availability of anti-bribery pledge form)
  4. የአሟላለሁ ወይም አላሟላም መግለጫ (Availability of Compliance statement)
  5. የ2018 ዓ.ም ግብር የከፈለ እና የታደሰ (2018 ዓ.ም) ንግድ ፈቃድ ያለው (Bidders should have a valid and renewed trade license for the year 2018 E.C)
  6. የቫት እና የቲን ሰርተፍኬት ማቅረብ የሚችል (Bidders should be VAT & Tin registered)

ማስታወሻ:-

  • መሥሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

ለበለጠ መረጃ ስልክ ቁጥር 046-180-32-07

ወሳይታ ሶዶ

ኢትዮ ቴሌኮም ደቡብ ደቡብ ምዕራብ ሪጅን ጽ/ቤት

✨ messages.ai_summary
Ethio Telecom seeks qualified bidders to supply construction electrical materials for its building in Arba Minch. Bidders must provide a bank-confirmed CPO, authorization letter, anti-bribery pledge, compliance statement, valid 2018 E.C. trade license, and VAT/TIN certificates.
Save Tender