የድሬዳዋ አስተዳደር ውሃና ፍሳሽ ባለሥልጣን 2018 በጀት ዓመት የምንጠቀምበት 10% ፈሳሽ ሶዲየም ሃይፖክሎራይት (sodium Hypocrite) በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለአንድ ዓመት ውል ፈጽሞ ለመግዛት ይፈልጋል።
ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
የድሬዳዋ አስተዳደር ውሃና ፍሳሽ ባለሥልጣን 2018 በጀት ዓመት የምንጠቀምበት 10% ፈሳሽ ሶዲየም ሃይፖክሎራይት (sodium Hypocrite) በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለአንድ ዓመት ውል ፈጽሞ ለመግዛት ይፈልጋል። እንዲሁም የእቃውን ጥራትና የአቅርቦት ብቃት ታይቶ ለተጨማሪ ለአንድ ዓመት የሚራዘም ይሆናል፡፡
ስለዚህ ቀጥሎ የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተወዳዳሪዎች በጨረታው እንዲሳተፉ ይጋብዛል፡፡
- የታደሰ ሕጋዊ ንግድ ፈቃድና አቅራቢዎች መታወቂያ ያላቸው።
- ቫት የተመዘገቡ እና የዘመኑን ግብር የከፈሉበትን ማስረጃ የሚያቀርቡ ቲን ቁጥር ያለው፡፡
- ከኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የገንዘብ ሚኒስቴር የስራው የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችል
- የጨረታው ዶክመንት የማይመለስ ብር 500 /አምስት መቶ ብር/ በመክፈል ድሬዳዋ እስተዳደር ውሃና ፍሳሽ ባለሥልጣን ከግዥ ፋይናንስና ደጋፊ የሥራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 05 በጥሬ ገንዘብ በመክፈል ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት እለት ጀምሮ በ15 ቀናት ውስጥ ሰነዱን መግዛት ይችላሉ።
- የጨረታ ሰነድ በውሃና ፍሳሽ ባለሥልጣን ቢሮ ቁጥር 05 ከ1፡30 እስከ 11፡30 ሰዓት ዘወትር በሥራ ሰዓትና ቀን መግዛትና ማስገባት ይቻላል።
- ጨረታው በማስታወቲያ በጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ15ኛው ቀን በ3፡00 ሰዓት የጨረታ ሳጥኑ ተዘግቶ በተመሳሳይ ቀን 3፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ጨረታው ይከፈታል፡፡
- ተጫራቾች ብር 60,000 (ስልሳ ሺህ ብር) ብቻ የጨረታ ማስከበሪያ በተረጋገጠ የባንክ ዋስትና ወይም CPO ከዋናው ሰነድ ጋር ማስያዝ አለባቸው።
- -የጨረታው ዶክመንት በታሸገ ፖስታ የእያንዳንዱ ዋጋና ጠቅላላ ዋጋ በግልጽ ማስቀመጥ አለበት በተጨማሪ በጨረታ ዶክመንቱ ውስጥ የተዘጋጁት ፎርማት ተሞልተውና ተፈርመው መቅረብ አለባቸው።
- -ያሸፈው ተጫራች የተጠየቀውን እቃ የግዥ ትዕዛዝ እንደተሰጠው በስፔስፊኬሽኑ መሠረት ተመላሽ በሚሆን ታንከር ወይም ጀሪካን በማሸግ በድሬዳዋ አስተዳደር ውሃና ፍሳሽ ባለሥልጣን የውሃ ማጣሪያ ጣቢያ ድረስ በየወሩ በማጓጓዝ ማቅረብ ይኖርበታል።
- በዶክመንቱ ከተሰጠው ስፔስፊኬሽን ወይም ሳምፕል የሚቀርብ ተቀባይነት የለውም።
- የጨረታው አሸናፊ ካሸነፈው በአንድ አመቱ ዋጋ 10% ውል ማስከበሪያ በተረጋገጠ የባንክ ዋስትና (CPO) ወይም በሁኔታ ያልተገደበ የባንክ ጋራንቲ ማስያዝ መስጠት የሚችል፡፡
- በጨረታው ሂደት ጨረታውን ለማዛባት ለማጭበርበር የሞከረ ተጫራች ከጨረታው ውጪ እንደሚሆንና በመንግሥት ግዥ እንዳይሳተፍ ይደረጋል።
- ጨረታ ሳጥኑ ከተዘጋ በኋላ የሚመጣ ጨረታ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፤
አድራሻ፡- ድሬዳዋ አስተዳደር ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን ድሬዳዋ
ስልክ ቁጥር፡- 0251124892 ፖ.ሣ.ቁ.446
የድሬዳዋ አስተዳደር ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን
