የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ፕሮጀክቶች ፖርትፎልዮ ማኔጅመንት ጽ/ቤት በስሩ ላሉ ቢሮዎች የ2017 በጀት ዓመት የሚያገለግሉ ቶነሮች ግዥ ለማከናወን በዘርፉ ከተሰማሩ ድርጅቶች በጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
በድጋሚ የወጣ የጨረታ ማስታወቂያ
ጨረታ ቁጥር EEU-PPM/07/2017(NCB)
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ፕሮጀክቶች ፖርትፎልዮ ማኔጅመንት ጽ/ቤት በስሩ ላሉ ቢሮዎች የ2017 በጀት ዓመት የሚያገለግሉ ቶነሮች ግዥ ለማከናወን በዘርፉ ከተሰማሩ ድርጅቶች በጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም ከዚህ በታች የተመለከቱትን መስፈርቶችን የሚያሟሉ ድርጅቶች በጨረታ መወዳደር ይችላሉ።
- ተጫራቾች የዘመኑን ግብር የከፈሉ መሆናቸውን የሚገልጽ ማስረጃ የሚያቀርቡና በመስኩ ህጋዊ ፍቃድ ያላቸው የታደሰ የንግድ ፈቃድ ፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ ፤ በኢፌዲሪ የመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ድህረ ገጽ በአቅራቢዎች ዝርዝር የተመዘገቡ ለመሆናቸው ማስረጃ ማቅረብ አለባቸው፣
- የጨረታ ሰነዱን ማስታወቂያው በጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ የማይመለስ ብር 300.00 (ሶስት መቶ ብር) በመክፈል በኢትዮጵያ ኤሌክትሪከ አገልግሎት የፕሮጀክቶች ፖርትፎሊዮ ማኔጅመንት ዳይሬክቶሬት ዋስትና የንግድ ማዕከል ህንፃ 11ኛ ፎቅ በመቅረብ መግዛት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ ብር 50,000 (ሃምሳ ሺ) በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ ወይም የዋስትና ጊዜው ከሚያበቃበት ቀን በኋላ 28 ቀን ተጨማሪ ጊዜ ያለውን የባንክ ዋስትና (Bank Guarantee) በኢ.ኤ.አ. ፕሮጀክት ፖርትፖልዮ ማነጅመንት ወይም EEU-PPM ስም ተዘጋጅቶ ከጨረታ ሰነዱ ጋር በሰንጠረዥ በተገለጽው ብር መጠን ማቅረብ አለባቸው::
- ተጫራቾች የሚወዳደሩባቸውን ዋጋ በታሸገ ኤንቨሎፕ በማድረግ እና ጨረታ ቁጥር EEU/PPM/NCB/07/2017 የሚል ምልከት በማድረግ እስከ ግንቦት 01 ቀን 2017 ዓ.ም እስከ ቀኑ 8:00 ሰዓት ድረስ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የፕሮጀክቶች ፖርትፎሊዮ ማኔጅመንት ዳይሬክቶሬት ዋስትና የንግድ ማዕከል ህንፃ 11ኛ ፎቅ ላይ በሚገኘው በግዥ ፈጻሚው መ/ቤት በመምጣት ለዚሁ ጨረታ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፣
- ጨረታው ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት /ባይገኙም ግንቦት 01 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 8፡30 ላይ ይከፈታል፣
- ስለጨረታው ዝርዝር መረጃ የጨረታ ሰነዱን ዘወትር በስራ ሰዓት ከሰኞ እስከ አርብ ጧት ከ2፡00-6:00 ከሰዓት 7፡00-11፡00 እና ቅዳሜ ጧት 2፡00-6፡00 ሰዓት መመልከት ይችላሉ ፡፡
- የፕሮግራም ጽ/ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው ፡፡
- ተጫራቾች መረጃ ከፈለጉ በስልክ ቁጥር 011-1-26-31-53 መደወል ይችላሉ፡፡
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የፕሮጀክት ፖርትፎሊዮ ማኔጅመንት ጽ/ቤት
