Tender Detail

Tender Details

  • Company በሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ
  • Address ሀዋሳ ከተማ ፡ ሲዳማ ክልል ፡ ኢትዮጵያ, Phone: 046-221-9988
  • Websitehttps://www.sbid.gov.et/
  • Deadline28 Sep 2026, 5:30 PM
  • magazineአዲስ ዘመን
  • Bid Document Priceብር 200.00 (በእያንዳንዱ ሎት የማይመለስ)
  • opening date በ11ኛው ቀን ከቀኑ 3፡30 ሰዓት
  • Categories Maintenance And Repair , Vehicle (Garage Service)

የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ለ2019 በጀት ዓመት የተሸከርካሪ ዓመታዊ ጥገና አገልግሎት በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡


በግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ 01/2019

የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ለ2019 በጀት ዓመት የተሸከርካሪ ዓመታዊ ጥገና አገልግሎት በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡

በዚሁ መሰረት በጨረታው መሳተፍ የምትፈልጉ ተጫራቾች የሚከተሉትን ማሟላት ይኖርባችኋል፡፡

  1. በሚወዳደሩበት ዘርፍ አግባብነት ያለውና ለዘመኑ የታደሰ የንግድ ፈቃድ፣ የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር፣ የዘመኑን ግብር ስለመከፈላቸው ከሚመለከተው አካል ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡
  2. በፌዴራል ግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ዌብ ሳይት የተመዘገቡ ስለመሆናቸው ከዌብ ሳይት አትመው ከጨረታ ሰነድ ጋር ማያያዝ የሚችሉ ወይም በክልሎች በአቅራቢነት ስለመመዝገባቸው የአቅራቢነት የምዝገባ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፣
  3. የግዥው መጠኑ ከብር 200,000 /ሁለት መቶ ሺህ ብር/ በላይ ከሆነ ለተጨማሪ እሴት ታክስ ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፣
  4. ጨረታው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ ሥራ ቀናት ለተጫራቾች ክፍት ሆኖ ይቆያል፡፡
  5. ተጫራቶች ጨረታው ክፍት ሆኖ በሚቆይበት ጊዜ ውስጥ በቢሮው የተዘጋጀውንና የጨረታውን ዝርዝር ሁኔታ የሚያሳይ የጨረታ ሰነድ የንግድ ፈቃዳቸውን በማሳየት ዘወትር በሥራ ሰዓት ቢሮ ቁጥር 7 ቀርበው በእያንዳንዱ ሎት የማይመለስ ብር 200.00/ሁለት መቶ ብር/ በመከፈል መውሰድና የመጫረቻ ሰነዶቻቸውን በአግባቡ በማዘጋጀት በፖስታ አሽገው ጨረታው ለተጫራቾች ክፍት ሆኖ በሚቆይበት ቀን እስከ 1፡25 ሰዓት ድረስ በቢሮው ቅጥር ግቢ ውስጥ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
  6. ጨረታው ክፍት ሆኖ በሚቆይበት የመጨረሻው ቀን 11፡30 ሰዓት ላይ ተዘግቶ ቀጥሎ ባለው በ11ኛው ቀን ከቀኑ 3፡30 ሰዓት ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በግዥ ፋይ/ንብ/ዳይሬክቶሬት ቢሮ ቁጥር 10 ይከፈታል፡፡ 10ኛው እና 11ኛው ቀን የሚውለው ቅዳሜና እሁድ ወይም የህዝብ በዓላት ቀን ላይ ከሆነ ጨረታው በሚቀጥለው የሥራ ቀን በ3፡00 ሰዓት ተዘግቶ 3፡30 ሰዓት ይከፈታል፡፡
  7. ተጫራቾች የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ስም ለጨረታው ማስከበሪያ የሚሆን ብር 10,000.00 /አስር ሺህ ብር/ ዋስትና በጥሬ ገንዘብ ወይም በሲፒኦ ወይም በባንክ የተረጋገጠ ዋስትና ማስያዝ ይጠበቅባቸዋል፡፡
  8. የፋይናንሻልና የቴክኒክ ሰነድና ሲ.ፒ.ኦ በተለያየ ፖስታ በማሸግ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡ የሚቀርበው የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና የጨረታው እየር ላይ መቆያ ጊዜ ከሚያበቃበት የመጨረሻው ቀን ጀምሮ ላሉት 45 ተከታታይ ቀናት የሚያገለግል መሆን ይኖርበታል
  9. አሸናፊው ተጫራች አሸናፊነቱ ከተገለጸበት በ 05 ቀናት ውስጥ አሸናፊ የሆነበትን የጥገና አገልግሎት ጠቅላላ ዋጋ 10% የውል ማስከበሪያ ሲ.ፒ.ኦ በመያዝ በ 15 ቀናት ውስጥ ለአንድ ዓመት የሚቆይ ጥገና ውል መግባት የሚችሉ መሆን አለበት፡፡
  10. ቢሮው የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊል ወይም ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

በስልክ ቁጥር 046-221-9988 / 046-220-03-26 በመደወል ማብራሪያ መጠየቅ የሚቻል መሆኑን እንገልጻለን፡፡

ሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ሀዋሳ

✨ messages.ai_summary
The Sidama National Regional State Industry Development Bureau seeks annual vehicle maintenance services via open tender. Bidders need a valid business license, tax registration and payment proof, federal or regional supplier registration, and VAT registration if the contract exceeds 200,000 birr.
Save Tender